About

Wednesday, December 2, 2020

ህዳር 24 ፃዲቁ አቡነ ተክለሃይማኖት


ህዳር 24 
አቡነ ተክለኃይማኖት 

❇️በዚች ቀን አባታችን አቡነ ተክለሀይማኖት በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም 10፣ 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡ በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል፡፡

❇️አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ
ቅዱስን መንበር እንዳጠኑ፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ
ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ሊቀ መላእክት
ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላቸው ነው በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ
እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ የነገራቸው። አባታችን አቡነ
ተክለ ሃይማኖትም መልአኩን ተከትለው ሐይቁን በእግራቸው
ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡

❇️እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ
እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም
ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኩሰዋቸዋል፡፡
ከዚህም በኋላ አባታችን በዚያው በሐይቅ በታላቅ ተጋድሎ
መኖር ጀመሩ፡፡ አክፍሎትንም በየሳምንቱ ያከፍላሉ፣ ከእሁድና
ከቅዳሜ በቀር ምንም አይቀምሱም ነበር፡፡ 

❇️በእነዚህም ዕለት
የአጃ ቂጣ ወይም የዱር ቅጠል ይመጉ ነበር፡፡ ወዛቸው እንደ
ውኃ ፈስሶ ምድሪቷን እስኪያርሳት ድረስ እስከ 70 ሺህ
ዓይነቱ ተጋድሎ ላይ ሳሉ ነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል
ድንገት ነጥቆ ወስዶ ከሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ያቆማቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ስለሆነው ነገር ራሳቸው አባታችን ተክለ ሃይማኖት
ሲናገሩ ‹‹…ከዚህ በኋላ መልአኩ ወደ ሰማይ አውጥቶ
ከመጋረጃው ውስጥ አስገብቶ ከሥላሴ ዙፋን ፊት አቆመኝና
ሰገድኩለት፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በማላውቀው በሌላ ምስጋና
አመሰገንኩት፡፡ ‹ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከ24ቱ ካህናቶቼ ጋር
ይሁን› የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ፡፡ የወርቅ ጽና
አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር አንድነት አጠንሁ፡፡ ምስጋናዬ
ከምስጋናቸው ጋር ልብሴም እንደልብሳቸው ሆነ፡፡ ፈጣሪዬንም
በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት፡፡ 

❇️በጸሎትህ የሚታመን ሰው ሁሉ
ስለአንተ ይድናል አለኝ…..›› (ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገጽ216-223)
ይህንን ታላቅ በዓል ነው ዛሬ የምናከብረው፡፡ አቡነ
ተክለሃይማኖት እንኳን አንደበታቸው የለበሱትም ልብሳቸውም
ጭምር እግዚአብሔርን በሰው አንደበት እንደሚያመሰግን
በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ አባታችን ለአቡነ ሀብተማርያምም በዚህ ክብራቸው እንዳሉ በአካል
ተገልጠውላቸዋል፡፡ ‹‹አቡነ ተክለሃይማኖት ከእርሳቸው በኋላ
በመንበራቸው ከተሾሙት ከስምንቱ መምህራን ጋር
ለሀብተማርያም ተገለጡላቸው፡፡ እነርሱም ኤልሳዕ፣ ፊሊጶስ፣
ሕዝቅያስ፣ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ፣ ዮሐንስ ከማ፣ እንድርያስና
መርሐ ክርስቶስ ናቸው፡፡ እነዚህም መልካቸው እንደ ፀሐይ
ያበራ ልብሳቸው እንደ መብረቅ ያንጸባርቅ ነበር፡፡ አቡነ ተክለ
ሃይማኖትም ልብሳቸው የእሳት ላንቃ የከበበው መልኩም ነጭ
የሆነ የሚያስደንቅ ሆኖ ‹በቅድምና ለነበረ ለአብ በቅድምና
ለነበረ ለወልድ በቅድምና ለነበረ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና
ይገባል› እያለ ልብሳቸው በሰው አንደበት ያመሰግን ነበር፡፡››
ተብሎ ነው በገድለ አቡነ ሀብተማርያም ላይ የተጻፈው፡፡

❇️ከዚህም በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ሀብተማርያም
ከተገለጡላቸው በኋላ ‹‹ልጄ ሀብተማርያም ሆይ! ፈጣሪዬ
እግዚአብሔር ስለወደደህ ብዙ ምርኮ እንዳገኘህ በአንተ ፈጽሞ
ደስ ይለኛል፡፡ ነገር ግን የምለምንህ ነገር አለና እሺ በለኝ
ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀበር ቃል ኪዳን ግባልኝ›› በማለት
በደጃቸው እንዲቀበሩ ቃል አስገብተዋቸዋል፡፡ በዋናነት ግን
ማየት የፈለኩት ጉዳይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሞት ካረፉ በኋላአቡነ ሀብተማርያ ደግሞ ገና በሕይወት ሳሉ አባታችን
ሲገለጡላቸው በምን ዓይነት ክብር እንዳዩአቸው ነው፡፡ 

❇️ ‹‹አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ልብሳቸው የእሳት ላንቃ የከበበው መልኩም
ነጭ የሆነ የሚያስደንቅ ሆኖ ‹በቅድምና ለነበረ ለአብ በቅድምና
ለነበረ ለወልድ በቅድምና ለነበረ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና
ይገባል› እያለ ልብሳቸው በሰው አንደበት ያመሰግን ነበር፡፡››
ጌታችን ለአቡነ ተክለሃይማኖት ‹‹ክፍልህ ከሃያ አራቱ ካህናቶቼ
ጋር ይሁን›› ብሎ አስቀድሞ ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋልና አባታችን
ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሆነው አንደበታቸውም ብቻ
ሳይሆን የእሳት ላንቃ ያለው ልብሳቸውም የሥሉስ ቅዱስን ስም እያመሰገነ ይኖራል፡፡ 

የአባታችን በረከታቸው ይደርብን ጸሎታቸው ያስምረን፡፡

No comments:

Post a Comment

ታህሳስ 6 ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ

GEDELEKIDUSAN ታህሳስ 3 ቅድስት አርሴማ(ቅዳሴ ቤቷ) ✝እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው።  ✝መድኃኒታችን ክር...