ህዳር 15
ቂርቆስ እየሉጣ
❇️ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሏት ዐበይት ሰማዕታት አንዱ ቅዱስ ቂርቆስ ነው። በተለይ በዘመነ ሰማዕታት ተነስተው እንደ ከዋክብት ካበሩትም አንዱ ነው።
ቅዱስ ወንጌል እንዲህ ይላል፦
"መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራል።"
(ማቴ. ፯፥፲፯)
❇️መልካም ዛፍ ቅድስት ኢየሉጣ መልካም ፍሬ ብፁዕ ቂርቆስን አፍርታ ተገኝታለችና ክብር ይገባታል። ቡርክተ ማኅጸንም እንላታለን። የተባረከ ማኅጸኗ የተባረከ ልጅን ለዘጠኝ ወር ተሸክሟልና።
❇️በዚያ ክርስቲያን መሆን መከራ በነበረበት ዘመን ይህንን ደግ ሕፃን እርሷን መስሎ እርሷንም አህሎ እንዲገኝ አስችላለችና። አበው በትውፊት እንዳቆዩልን ከሆነ በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዚህች ቀን እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ብጹዕ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስን ወልዳለች።
ፈጣሪ ቢያቆየን የሰማዕትነት ዜናቸውን ጥር ፲፭ ቀን የምንመለከት ነንና የዚያ ሰው እንዲለን እንማጸነዋለን።
❇️አምላከ ሰማዕታት በምሕረቱ ይማረን። በይቅርታው ኃጢአታችን ይተውልን። ከበረከተ ሰማዕታትም ይክፈለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
No comments:
Post a Comment