ህዳር 16
ቅድስት ጣጡስ ሰማዕት
❇️በቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደዚህች ቅድስት ወጣት መልከ መልካም አልነበረም።
❇️ቅድስት ጣጡስ በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን (በዘመነ ሰማዕታት) የነበረች ሮማዊት ክርስቲያን ስትሆን መልኳን ያየ ሁሉ ይደነቅ፣ ይደነግጥም ነበር።
❇️እርሷ ግን ለወንድሞቿ እንቅፋት እንዳትሆን በፊቷ ላይ ዓይነ ርግብ ጣል አድርጋና እንደ ነገሩ ለብሳ ትኖር ነበር። (እንዲህ ነበሩ እናቶቻችን!) ታዲያ በዘመኑ እስክንድሮስ የሚባል አረማዊ "ለጣዖት ስገዱ።" እያለ ክርስቲያኖችን ሲገድል የእርሷ ተራ ደረሰ።
በዐውደ ስምዕ (በምስክርነት አደባባይ) ላይ አቁሟት "ፊቷን ግለጡልኝ።" አለ። ቢገልጧት ከመልኳ ማማር የተነሳ ፈዘዘ።
❇️እጅግ በመፍጠንም "ላግባሽ?" አላት። "ሙሽርነቴ ሰማያዊ ነውና አይሆንም!" አለችው። ለመናት አልሰማችውም። አስፈራራት አልደነገጠችም።
ከዚያ ግን አስገረፋት። ከአካሏም ስለ ደም ፈንታ ወተት ፈሰሰ። ተበሳጭቶ ለአራዊት ጣላት። እነርሱ ግን ሰገዱላት። በእሳትም ፈተናት። እርሷ ሁሉንም ታግሣ ጸናች። በመጨረሻው ግን በዚህች ቀን አስገደላት። ፈጣሪዋ ክርስቶስም በሰማያዊ አክሊል ከለላት።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
No comments:
Post a Comment